በቡራዩ ከተማ በህገ ወጥ መንገድ ለኦነግ ሸኔ ሊተላለፍ የነበረ ለፀጥታ አካላት ብቻ የተፈቀደላቸው ቀበቶና የመሣሪያ ጥይቶች በቁጥጥር ሥር ዋሉ
በቡራዩ ከተማ አስተዳደር ልዩ ቦታ ገፈርሳ ኖኖ ተብሎ የሚጠራ ቦታ መነሻ አዲስ አበባ ጎጀም በረንዳ ያደረገ ለሸኔ ወደ ምስራቅ ወለጋና ምዕራብ ወለጋ ሊላክ የነበረ 2656 ለፀጥታ አካላት ብቻ የተፈቀደላቸው ቀበቶና 4143 የክለሽንኮቪ ጥይቶች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገለፀ።
ከህገወጥ ቀበቶና ጥይቶቹ ጋርም 5 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥሪ መዋላቸውን በቡራዩ ከተማ አስተዳደር ፖሊሲ መምሪያ የወረዳ 1 ፖሊስ ፍትህ መስጠት የሥራ ሂደት ባለቤት ሳጅን ሙሉነህ ቃናዓ ገልጸዋል።
@YeneTube @FikerAssefa