Get Mystery Box with random crypto!

መንፈሳዊ ኪነ-ጥበብ💒

Logotipo del canal de telegramas menfesawigetem - መንፈሳዊ ኪነ-ጥበብ💒
Logotipo del canal de telegramas menfesawigetem - መንፈሳዊ ኪነ-ጥበብ💒
Dirección del canal: @menfesawigetem
Categorías: Religión
Idioma: Español
Suscriptores: 9.70K
Descripción del canal

በተለያዩ ሰዎች የተፃፋትን መንፈሳዊ ግጥም እና ታሪክ የኪነጥበብ ፅሁፎችን መንፈሳዊ profile Picture አሰተማሪ ታሪኮችን የሚያገኙበት channel ነው👈

በሰነፍ ጆሮ አንዳች አትናገር፣የቃልህን ጥበብ ያፌዝብሀልና። ምሳሌ 23፥9

መንፈሳዊ ግጥም ታሪክ ጭውውት ድራማ ለመላክ
t.me/abrex_1 @yemaryamlj1
ላይ መላክ ይቻላል አሰተያየት እንቀበላለን

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


Los últimos mensajes 2

2023-05-14 12:59:10
አላፍርም እኔ በማርያም | ዘማሪት አዜብ ከበደ | alaferem ene bemaryame | azeb kebede new orthodox mezmur
924 viewsWÊÑDÏ , 09:59
Abrir / Cómo
2023-05-14 08:36:48 መንፈሳዊ ኪነ-ጥበብ pinned «ሌሎች መንፈሳዊ ግጥሞች እና የተለያዩ የኪነጥበብ ስራዎችን ለማግኘት ከላይ ያለውን forward በመንካት ወይም ከስር ያለውን link በመንካት ቻናላችንን ይቀላቀሉን @menfesawigetem መንፈሳዊ መነባነብ ሰአሊለነ ቅድስት አረ አልሆንልኝ አለ መንፈሴ አልገዛም አለ የጭንቅ አማላጂቱ አንድ ብትዪኝ ምንአለ ፀሎት ምህላ አቃተኝ መንፈሴ ለንሰሀ ሸፈተ መንፀፈዴይን ወደኩኝ ነፈሴ በሀጥያት ሸተተ።…»
05:36
Abrir / Cómo
2023-05-14 08:36:11 ሌሎች መንፈሳዊ ግጥሞች እና የተለያዩ የኪነጥበብ ስራዎችን ለማግኘት ከላይ ያለውን forward በመንካት ወይም ከስር ያለውን link በመንካት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@menfesawigetem

መንፈሳዊ መነባነብ

ሰአሊለነ ቅድስት

አረ አልሆንልኝ አለ መንፈሴ አልገዛም አለ
የጭንቅ አማላጂቱ አንድ ብትዪኝ
ምንአለ
ፀሎት ምህላ አቃተኝ መንፈሴ ለንሰሀ
ሸፈተ
መንፀፈዴይን ወደኩኝ ነፈሴ በሀጥያት ሸተተ።
እምቢ አለኝ ፆም ፀሎት እምቢ አለኝ
ንሰሀ
ስጋ መንፈሴ ኮብልሎ እየዋኝ ከእለም ውሀ።
አረ አንድ በይኝ እመቤቴ ወለላይቱ
ተማለጂኝ
ጨርሶ አለም ሳይነጥቀኝ ከወቅኩበት
አንሺኝ።
ነጭ ነጠላ አጣፍቼ ከቤተ መቅደስ ሰዎጣ
መፀሐፍ ቅዱስ ዘርግቼ ለስብከት
መድረክ ስዋጣ፡፡
ልበሰ ተክኖ ለብሼ ነፍቅ ገባሬ ሰናይ
ሲሆን
ጥቅስ በቃሌ ስደረድር ለዜማ ቅኔ ስቀኝ
አካሌ እዚ ሆኖ መንፈሴ እየሸፈተ
ነፍሴን በሀጥያት ገንዞ ስጋዬ ነፍሴን ጎተተ፡፡
አረ አንድ በይኝ እመብረሀን ወለላይቱ
ተማለጂኝ
ጨርሶ አለም ሳይዎስደኝ ከወደኩበት
አንሺኝ
ማለዳ ኪዳን አድርሼ ቅዳሴ ፀሎት
ጨርሼ
ከቤተክርስቲያ ወጥቼ ወደ ስጋ ገበያ ተመልሼ።
በሀጥያት ባህር ስዋኝ የግፍ ዳንኪራ
ሰረግጥ እውላለው
የልጅነት ፀጋዬን አውጥቼ ብኩርናዬን
እሸጣለው።
እዚህ መላክ መስዬ ላዬ በቅድስና በርቶ
ውጪ ከክፋት ከፍቼ ሀጥያት በፅድቅ
ተተክቶ።
በሀሜት የሰው ስጋ ስበላ በወንድሜ
ሸር ስሸርብ
ሰዋሽ ሰቀጥፍ ውዬ ስሰርቅ ሳሽሟጥጥ ስሳደብ።
ነጠላ ስለብስ ግን ወደ ቤተ
እግዚአብሔር ስገባ
ሰአሊለን ቅድስት ስል ያለ ንሰሀ እንባ።
የመውደቂያዬ ጉድጓዱ ጥልቀቱ ወሰን
ዳርቻ የለው
አዝነ ህሊናዬ ለአለም እጂ ለፅድቅ ቦታ
የለው፡፡
ማሀረነ ክርስቶስ እንዳልል ተዘከረነ ፈጣሪዬ
ሀጥያቴ በደሌ አፈነኝ በሀፍረት ነደደ ህሊናዬ።
ምን ብዬ ልጥራው ጌታዬን ተዘከረነ ብዬ
ስለኔ መገረፉን የመስቀሉን ፍቅር አቃልዬ
እንዴት ማረኝ ልበለው ስለ ስጋ ጣዕም
ተቃጥዬ።
ምንብዬ ልጥራው ጌታዬን
አይኔን ወደጠፈጠፍ ሰማይወደስላሴ መንበር
አንስቼ ማየት አቃተኝ ማረኝ ብዬ ለመናገር።
ለሰው ፃዲቅ መስዬ የሀጥያት ጎተራ ሆኛለው
እንዴት አባቴ ቀናብዬ መንበረ ፀባኦትን አያለው።
እባክሺን እናቴ ወለላይቱ ተማለጂኝ
እንደ ቃና ዘገሊላ ባዶ ማደጋዬን ሙይልኝ።
ከፊቱ እንዳላፍር ከአማኑኤ ጋር አስታርቂኝ
ለተጠማው ውሻ እንዳዘንሽ ለመፃተኛው እዘኚልኝ።
አንቺ የቱሁታን ትሁት ርሪሂተ ልብ እናቴ
ከልጅሽ ከእየሱስ አማልጂኝ እዘኚልኚ እመቤቴ
አንቺ ውዳሴሽ የነፍስ ስንቅ ስምሽ ከማር የጣፈጠ
በላዬሰብ በእልፍኝ ውሀ በምልጃሽ ከሞት ያመለጠ
አንቺ
መላእክት የሚጎበኙሽ የካህናት አለቆች ምስጋናቸው
በመወሰን የማይዎሰን እሳተ መለኮት የቻልሺው።
አንቺ
ከገነት በተሰደደ ጊዜ ለአዳም ተስፋ የሆንሺው
ዛሬም ለኔ ተስፋ ሁኚ ለነፍሴ ስለነፍሴ ተዋሺው።
እንጂ እኔማ አልቻልኩም የነፍሴ ንፅህና ጠፍቷል
ለፀሎት እንኳን ስቆም ልቤ ለሁለት ተከፈሏል።
አረ አልሆነልኚም መንፈሴ አልገዛም አለ
የጭንቅ እማላጂቱ አንድ ብትይኝ ምን አለ
እምቢ አለኝ ፆም ፀሎት እምቢ አለኝ ንሰሀ
ስጋ መንፈሴ ኮብልሎ እየዋኝ ከአለም ውሀ።
የልቤን መዎላዎል የነፍሴን ድካም አበርቺ
በአማላጅነትሽ ስር ነኝእና ከልጅሽ አስታርቂኝ አንቺ።
ለሰው አይን ባይገለፅም ሰውሬ የሰራሁት ሀጥያት
አምላክን አሳዝኖታል የምኖርበት ህይዎት።
ይሀው
የምናገረው አይሰምር የዎረወርኩት አይመታም
ስጋዬ አልተቀደሰ ገበታዬ በረከት የለውም።
እውቀት ምርምር አይዘልቀኝ ህሊናዬ ፍሬ አይቋጥር
ዝሩ ሆኖ ቀርቶብኝ የነፍስ የስጋዬ ሚስጥር።
ይሀው
የማዎራው ለሰው አይጥምም ፍቅር ከኔ ቤት ርቋል
መቆም መቀመጤ አያምር ሰው በስራዬ ይማረራል።
የሀጥያት ምንዳዬ ይሀው የሀጥያት ደሞዜ ይሀው ስቃይ ውስጤን በልቶታል
ለአንድነት የተናገርኩት ዛሬም ጉባኤ ይበትናል።
እና አዛኚቱ ታረቂኝ ከልጅሽ ከአማኑኤል አማልጂኝ
ከሰው የሸሸኩት ሀጥያት ጨርሶ በልቶ ሳይዉጠኝ
የበላዬሰብ እመቤት እባክሽን ተማለጂኝ
አንቺ ህይዎቴን ዳብሺው ነፍሴ ህይዎት እንድታገኝ
አረ አልሆነልኝም መንፈሴ አልገዛም አለ
የጭንቅ አማላጂቱ አንድ ብትይኝ ምን አለ
ፀሎት ምህላ አቃተኝ መንፈሴ ለንሰሀ ሸፈተ
መንፀፈዴይን ወደኩኝ ስጋዬ ነፍሴ ሸተተ
እምቢ አለኝ ፆም ፀሎት እምቢ አለኝ ንሰሀ
ስጋ መንፈሴ ኮብልሎ እየዋኝ ከአለም ውሀ
አረ አንድ በይኝ እመቤቴ ወለላይቱ ተማለጂኝ
ጨርሶ አለም ሳይነጥቀኝ ከዎደኩበት አንሺኝ

እባክሺን ተማለጂኝ እናቴ ኪዳነ ምህረት
ተስፋ ክብራችን አንቺ ነሽ
ሰአሊለነ ቅድስት
ሰአሊለነ ቅድስት

መንፈሳዊ ኪነ-ጥበብ

በማርያም በእመብረሀን ሼር ሊንክ አድርጉ
2.6K viewslog out, edited  05:36
Abrir / Cómo
2023-05-13 21:11:36 ወዳጄ ፈጣሪህን አስቀድም!

ወዳጄ አንዳንድ በሮች ይዘጉብሀል፤ ለምን ካልከኝ ቦታህ ስላልሆኑ፣

ወዳጄ አንዳንድ በሮች ይዘጉብሀል፤ ለምን ትለኝ እንደሆነ ጥንካሬህን ሊፈትኑ፣

ወዳጄ አንዳንድ በሮች ይከፈቱልሀል ፤ ለምን ካልከኝማ ያንተ ስለሆኑ፣

ወዳጄ አንዳንድ በሮች ይከፈቱልሀል ፤ ለምን ትለኝም እንደሆነ በግድ ስለታገልካቸው፣

ወዳጄ እናም ተዘጋ ማለት በቃ ማለት ብቻ አይደለም ተከፈተም ማለት ሆኗል ማለት አይደለም እናም አስተውልና ከፈጣሪህ ጋር ተማክረህ መንገድህን ቀጥል ከፊትህም ፈጣሪህን አስቀድም።

ሰናይ ለሊት
1.4K viewsBirta, 18:11
Abrir / Cómo
2023-05-13 13:00:18 #አለማዉያንን_ወደ_መንፈሳዊነት_ማምጫ_ወጥመድ


ብዙ ጊዜ ሰዎች ወደ መንፈሳዊነት እንዳይመጡ ጣጣ እናበዛቸዎለን ሰንበት ትምህርት ቤት "ሱሪ ከአሁን በኋላ ግን መልበስ የለብሽም፣ ፀጉርህን መጀመሪያ ተስተካከል መጀመሪያ ዘፈን ማዳመጥም መዝፈንም አቁም" ምናምን ምናምን እያልን እናስጨንቃቸዎለን ወዳጆቼ እኔ ሴት ሱሪ መልበሷ ምንም ችግር የለውም ወንድ ፀጉሩን ማሳደጉ መልካም ነው አላልኩም ዘፈንም መዝፈንና ማድመጣችን ጌታን ያስደስተዎል አልወጣኝም ግን መጀመሪያ ይምጡ የጌታ ቃል ኃይል አለው አንድ ቀን ልባቸው በጌታ ፍቅር ይማረካል ብዙዎቻችን የምንሸወደው ተስተካክዬ ቤተ ክርስቲያን እሄዳለሁ ሰንበት ትምህርት እገባለው ስለምንል ነው ግን አደለም የምንስተካከለው ቤተ ክርስቲያን ስንሄድ ነው ሱሪ ለሚለብሱ እህቶቻችሁ የጌታን ቃል ንገሯቸው ለምን ኃጢአት እንደሆነ አስረዷቸው ጉርድ ለብሰው ወደ ቤተክርስቲያን አብረዋችሁ እንዲሄዱ አድርጉ። ተምራችሁ ስትመለሱ ጉርዱን አዉልቃ በሱሪ ወደሌላ ቦታ ብትሄድ በጥላቻ መንፈስ ፊታችሁን አኮሳትራችሁ አትመልከቷቸው
እስኪ አንድ ቆንጆ የሀይዌስት ጉርድ ካላቹ አንዱን ስጧት ለብሳው ስታዩዋት እንዴት እንዳማረብሽ ብላችሁ ፈገግ ብላችሁ ንገሯት ውበቷን አድንቁላት ያው ክርስቲያናዊ በሆነ መንገድ ማለቴ ነው። እንደ ዉሀ ቀላል እንደ ድንጋይ ጠንካራ የለም ታቃላቹ ድንጋይ ላይ የውሀ ጠብታ በተደጋጋሚ ቢያርፋበት ድንጋዩ ይሰነጠቃል (ቀላሉ ውሀ ጠንካራውን ድንጋይ መስበር ከቻለ ግሩም ድንቅ የሆነውን የጌታ ቃል የኛን ልብ መቀየር ወይም ማሸነፋ እንደሚችል ትጠራጠራላችሁ?) ደሞ እኛ ፀጉራችንን እንደሚገባ ተቆርጠን( ተስተካክለን) ይሆናል መልካም ደስ ይላል ግን እኮ ውስጣችን ላይ ብዙ ያልተስተካከለ ነገር አለን ታድያ አንድ ወንድማችን ፀጉሩ ስላደገ ብቻ ቤተክርስቲያን ለመምጣት መጀመሪያ ተስተካከል ብለን ለመምጣት እንዲፈራ ልናደርገው ይገባል? ቅዳሴ እስኪ ውሰዱት ምን አልባት እናንተ ብዙ ጊዜ ስላስቀደሳችሁ መንፈሳዊ ልምምድ ስላደረጋችሁ ሙሉ ቅዳሴ ቁማችሁ ታስቀድሱ ይሆናል ግን አዲሱ አስቀዳሽ ወንድማችሁ ሙሉውን መቆም ይከብደው ይሆናል እኔ ግን አልችልም የሚል ስሜት እንዳይሰማው በመሀል በመሀል ቁጭ በሉ ወንጌል ሲነበብ.... መቆም ባለባችሁ ጊዜ ቁሙ ያኔ ካንተ እንደማያንስ ይገባዋል ቀስ በቀስ ይለማመዳል ከዛ በመንፈሳዊነት እጅጉን ይበረታል እንዲሁም አንዳንዶች ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ተማሪዎች ፣የዲያቆናት፣ የቀሳውስት ፣የጳጳሳት ብቻ መስሎ ይሰማቸዋል እስኪ የእነሱም እንደሆነች እንዲገባቸው እናድርግ። በቤተክርስቲያን እንደ አገልግሎታችን ማዕረጋችን ይለያይ እንጂ ሁላችንም እኩሎች ነን። ይሄን እንዲረዱ በተግባር እናሳያቸው ሰንበት ትምህርት ወስደን ከበሮ እናለማምዳቸው ነጠላ አልብሰን ነጠላው ምን ያክል እንዳማረባቸው እንንገራቸው በፍቅር እንያቸው ክርስትና ስማቸውን ጠይቀን እንፀልይላቸው ጌታ ሆይ ይህ ወንድሜን ይህች አህቴን ወደ መንፈሳዊ ህይወት እንድትገባ እርዳት በሉት ጌታ ለአንዲት ነፍስ እንኳ መጨነቃችሁ ደስ ያሰኘዋል ፀሎታችሁን ይሰማችኋል። የናንተንም ክርስትና ስም ነግራችሁ ለወንድማችሁ ወይም እህታችሁ እንዲፀልዩላችሁ ንገሯቸው አይ እኔ እንዴት ላንተ እፀልያለሁ አንተ ነህ ወደ ጌታ የቀረብከው ሲሉን ጌታ በደንብ እንደሚሰማቸው ኃጢአታችን እንጂ እኛን መቸም እንደማይጠላን እናስረዳቸው በሌላ ቀን ወንድሜ እየፀለይክልኝ?ነው እህቴ እየፀለይሽልኝ ነው? ኧረ እባክህ አትርሳኝ በሉት። ለወንድም እህቶቻችሁ መዳን የማትጨነቁ ከሆናችሁ የእውነት አልዳናችሁም ማለት ነው (ለወንድሙ መዳን የማይጨነቅ ሰው እኔ ድኗል ብዪ አላስብም እንዳለ አባታችን ቅዱስ ዮሀንስ አፈወርቅ) በእውነት የእህት ወንድሞቻችን ህይወት ካላስጨነቀን ምን አልባት ስለ ክርስቶስ እናቅ ይሆናል እንጂ ክርስቶስን አናውቀውም ማለት ነው የጌታ ፍቅር ገና አልገባንም ማለት ነው ለሰዎች መዳን ምክንያት እንድንሆን ጌታ ይርዳን


ወስብሀት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር ይቆየን።
1.6K viewsWÊÑDÏ , 10:00
Abrir / Cómo
2023-05-12 13:43:21 *ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ*

*ጥር 4 እንኳን ለወንጌላዊ ቅዱስ ዮሐንስ ዓመተ ክብር በዓል በሰላም አደረሰን!*

*በዚህች ቀን ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ሞትን ሳይቀምስ ወደ ብሔረ ሕያዋን የተሰወረበት ታላቅ በዓል በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ይከበራል::*

*ከአባቶቹ ነብያት ከወንድሞቹ ሐዋርያት መካከል እንደ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ምስጢረ ሥላሴን አምልቶ አስፍቶ የተናገረ የለም::*

*ከመስቀል ስር ያልተለየ ብቸኛ ሐዋርያ ቅዱስ ዮሐንስ ነው::*

*እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን በአደራ የተቀበለ  እና በቤቱ  ልጅ ሆኗት 15 ዓመት አብሯት የኖረ ይህ ታላቅ ሐዋርያ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ነው::*

*መልኩ ጌታችንን ይመስል ነበር፤ ለዚህም ነበር ይሁዳ ጌታን በመሳም ለአይሁድ አሳልፎ የሰጠው መልካቸው ስለሚመሳሰል ተሳስተው ዮሐንስን እንዳይዙት ነበር::*

*ስለዚህ ሐዋርያ ስንቱን እንናገር ብዙ መከራ ተቀብሏል። ነገር ግን እንደ ወንድሞቹ ሐዋርያት ደሙ ፈሶ በሰማዕትነት አይደለም ያረፈው፤ በ 90 ዓመቱ በዛሬዋ ቀን *ከነሥጋው ተሰወረ* *እንጂ በረከቱ ይደርብን።*

' *በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ። …ቃልም ሥጋ ሆነ” የሚለውን ታላቅ ምስጢረ ቤተ ክርስቲያን በወንጌሉ የመጀመሪያ ምዕራፍ ላይ የጻፈልን እርሱ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ነው::*

*ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌሉን የጻፈው በኤፌሶን ነው ዘመኑ መቼ ነው ቢሉ ጌታ ባረገ በ 30 ዓመቱ፤ የጻፈበት ቋንቋም ጽርዕ ይባላል::*

*እናም ወንጌሉን ሲጽፍ በመጀመሪያ ቃል ነበር ብሎ መጻፍ ሲጀምር ራዕይ ያያል: ከዋነኞቹ መላአክት አንዱ ከትልቅ ውቅያኖስ ዳር ቁጭ ብሎ የውቅያኖሱን ውኃ በእንቁላል ቅርፊት እየጨለፈ ወደ መሬት ያፈሳል:: ቅዱስ ዮሐንስ ጠጋ ብሎ ምን እየሰራህ ነው ? ይለዋል የውቅያኖሱን ውኃ ወደ መሬት እፍስሼ ለመጨረስ ነው ይለዋል:: ይህ እንዴት ይሆናል? ደግሞም በእንቁላል ቅርፊት? ቢለው:: ይህ ውቅያኖስ ፍጡር ነው ከረጅም ዘመን በኋላ ሊሳካልኝ ይችላል:: አንተስ አለህ አይደል ቢቀዱት የማያልቀውን ቢጀምሩት የማይጨርሱትን የመለኮት ነገር  ለመጻፍ* *በመጀመሪያ ቃል ነበር* *ብለህ የተነሳህ?አለው::*

*በዚህ ጊዜ ነው ቅዱስ ዮሐንስ የጀመረውን አቁሞ ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን። ብሎ ወደ ምስጢረ ሥጋዌ የገባው ዮሐ 1፤14።*

*ዮሐንስ ማለት የስሙ ቀጥተኛ ትርጉም*  *እግዚአሔር ጸጋ ነዉ ወይም ደስታ ነው ማለት ነዉ* ፡፡

*አባቱ ዘብዴዎስ ፤ እናቱ ማርያም ባዉፍልያ ይባሉ ነበር፡፡*

*ቁጥሩ ከዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት የሆነ ያዕቆብ የተባለ ወንድም ነበረዉ፡፡ ማቴ 4፡21 ፤ ማር 1፡20 ፤ማቴ 20፡20*

*ቅዱስ ዮሐንስ አስቀድሞ የዮሐንስ መጥምቅ ደቀ መዝሙር ነበር፡፡ ዮሐ 1፡ 35*

*ቅዱስ ዮሐንስ ከአባቱና ከወንድሙ ጋር ዓሣ በሚያጠምድበት በገሊላ ባህር ላይ መረቡን ሲያበጅ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሐዋርያነት ጠራዉ፡፡ እሱም አባቱን ሌሎቹን ቤተሰቦቹንና ታንኳውን ትቶ ከወንድሙ ያዕቆብ ጋር ጌታን ተከተለዉ፡፡*

*ቅዱስ ዮሐንስ ሲያስተምር ድምጹ እና ሀይሉ ታላቅ ነበርና ቦአኔርጌስ ወይም ወልደ ነጎድጓድ ተብሏል፡፡*

*ለጌታችን በጣም ቅርብ ከነበሩት ሦስት የምሥጢር ሐዋርያት (ጴጥሮስ ፤ያዕቆብ ዮሐንስ) ቀዳሚዉ እርሱ ዮሐንስ ነዉ፡፡*

*ጌታችን ምሥጢረ ተአምራትን በኢያኢሮስ ቤት ምሥጢረ መንግስትን (መለኮትን) በደብረ ታቦር* ፣ *ምሥጢረ ምጽአትን በደብረ ዘይት ፣ ምሥጢረ ጸሎትን በጌቴ ሴማኒ ሲገልጽና ሲያሳይ አብሮ የተመለከተ  ታላቅ ሐዋርያ ነው ቅዱስ ዮሐንስ ፍቁረ እግዚእ* ::

*ስለ እርሱም በታላቁ መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹ጌታ ይወደዉ የነበረ ደቀ መዝሙር ››ተብሎ ስለ ተጠቀሰ የጌታ ወዳጅ  ወይም ፍቁረ እግዚእ ይባላል፡፡ዮሐ 13፡ 23 ፡፡*

*ቅዱስ ዮሐንስ እስከ መስቀል ድረስ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቀበለዉን መከራ በአየኖቹ በማየቱ ከታላቅ ኃዘኑ የተነሳ ከዚያ ዕለት ጀምሮ 70 ዘመን ሙሉ ፊቱ በኅዘን የተቋጠረ በመሆኑ (ቁጽረ ገጽ) ሆኖ ኖሯል፡፡*

*ቅዱስ ዮሐንስ ምሥጢረ ሥላሴንና ምሥጢረ ሥጋዌን አምልቶና አስፍቶ በመጻፉ (ታኦጎሎስ) ተብሏል፡፡ትርጉሙም ነባቤ መለኮት (የመለኮትን ነገር የሚናገር)ማለት ነዉ፡፡*

*ፍጥሞ በምትባል ደሴት ላይም ወደ ፊት የሚሆነዉን ነገር በራእይ ስለተገለጸለት በግሪክ ቋንቋ አቡቀለምሲስ ተብሏል፡፡ትጉሙም የራእይ አባት ማለት ነዉ፡፡*

*ቅዱስ ዮሐንስ የዮሐንስ ወንጌልን በመጻፉ ወንጌላዊ ተብሏል፡፡*

*በቅድስት ሥላሴ ስዕል ላይ ካሉት አራቱ እንስሳ አንዱ ንስር ነዉ፡፡ንስር በእግሩ ይሽከረከራል በክንፉ ይበራል፡፡ንስር በእግሩ እንደመሽከርከሩ ቅዱስ ዮሐንስም የክርስቶስን ምድራዊ ታሪኩን ጽፏል፡፡ንስር በክንፉ መጥቆ እንደሚበር ቅዱስ ዮሐንስም ከሌሎቹ ወንጌላዉያን ለየት ብሎ የመለኮትን ሰማያዊ አኗኗር ጽፏል፡፡ንስር አይኑ ንጹህ ነዉ ሽቅብ ወጥቶ ቁልቁል ሲመለከት ቅንጣት የምታክል ሥጋ አታመልጠዉም፡፡ቅዱስ ዮሐንስም ወንጌል ሲጀምር እጅግ ርቆና መጥቆ የሥላሴን አንድነትና ሦስትነት የአካላዊ ቃልን (የእግዚአብሔር ወልድን)በቅድምና መኖር ተናግሯል፡፡በዚህም ዮሐንስ ዘንስር ተብሏል፡፡*

*ከሐዋርያት መካከል ሞትን ያልቀመሰ በህይወተ ሥጋ እያለ ወደ ሰማይ የተነጠቀ እንደ ሔኖክ ፣እንደ ኤልያስ በብሔረ ሕያዋን የሚኖር ሐዋርያ ነዉ፡፡*

*ጌታችንም ለቅዱስ ጴጥሮስ ‹ዮሐንስ እኔ እስክመጣ ድረስ በሕይወት ይኖር ዘንድ ብወድስ ምን አግዶህ?›ዮሐ 21፡20 ብሎታል ይህም እስከ ምጽአት ድረስ እንደሚኖር መናገሩ ነዉ፡፡በማቴ 16፡18 ላይ ‹‹እዉነት እውነት እላችኋለሁ በዚህ ከቆሙት ሞትን የማይቀምሱ አንዳንድ አሉ›ያለዉ ቃል ለቅዱስ ዮሐንስና መሰሎቹ የተነገረ ቃል ነዉ፡፡*

*የቅዱስ ዮሐንስን ታላቅ ክብር በማሰብ እውነተኛይቱ ቅድስት ቤተክርስቲያን 365 ቀን ዓመቱን በሙሉ በየዕለቱ ጠዋት ጠዋት ተአምረ ኢየሱስ  ተነቦ ሲያልቅ እንዲህ እያለች ቅዱስ ዮሐንስን ልብ በሚመስጥ ያሬዳዊ ዜማ ታመሰግነዋለች:*

ሰላም ለከ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ
ሰላም ለከ ዮሐንስ አቡቀለምሲስ
ሰላም ለከ ዮሐንስ ታኦጎሎስ
ሰላም ለከ ዮሐንስ ፍቁረ እግዚእ
ሰላም ለከ ዮሐንስ ድንግል
ሰላም ለከ ዮሐንስ ወንጌላዊ
ሰላም ለከ ዮሐንስ ዘረፈቀ ውስተ ሕጽኑ ለኢየሱስ

*የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በረከቱ ረድኤቱ ከሁላችን ጋር ይሁን*

*ብሩህ ቀን*
1.8K viewsWÊÑDÏ , 10:43
Abrir / Cómo
2023-05-12 13:28:57 ወዳጄ ሆይ! ኃጢአተኛ ከኾንህ በደልህን ትናዘዝ ዘንድ ወደ ቤተ ክርስቲያን ና፤ ጻድቅም ከኾንህ ከጽድቅ [ጎዳና] እንዳትወድቅ ወደ ቤተ ክርስቲያን ና፤ ቤተ ክርስቲያን የኃጥኡም የጻድቁም ወደብ ናትና፡፡

ኃጢአተኛ ነህን? ተስፋ አትቁረጥ፤ ወደ ቤተ ክርስቲያን መጥተህም ንስሐ ግባ፡፡ ኃጢአት ሠርተሃልን? እንግዲያውስ እግዚአብሔርን “በድያለሁ” በለው፡፡

እስኪ ንገረኝ! “በድያለሁ” ብለህ ለመናዘዝ ምን ውጣ ውረድ፣ ምን ዓይነት የሕይወት መርሕ፣ ምንስ መከራ አለው? “በድያለሁ” ብሎ አንዲት ቃል ለመናገር ክብደቱ ምኑ ላይ ነው? ምናልባት [ኃጢአት ሠርተህ ሳለ] በደለኛ አይደለሁም የምትል ከኾነ ዲያብሎስም አንተን አይወቅስህም፡፡ [በድያለሁ ብለህ ንስሐ የምትገባ ከኾነ ግን] ይህን [ዲያብሎስ ሊወቅስህ እንደሚችል] አስቀድመህ አስብ፡፡ …

ስለዚህ ክብርህን እንዳይወስድብህ ለምን አትከለክለውም? ለቅጽበት ያህልስ እንኳን የማይተኛ ከሳሽ እንዳለህ ዐውቀህ ለምን በደልህን ተናዝዘሃት አታስወግዳትም?

ኃጢአት ሠርተሃልን? እንግዲያውስ ወደ ቤተ ክርስቲያን መጥተህ እግዚአብሔርን “በድያለሁ” ብለህ ንገረው፡፡ እኔ ከዚህ ውጪ ከአንተ የምፈልገው ሌላ ምንም ነገር የለኝም፡፡
መጽሐፍ ቅዱስም፡- “ንግር አንተ ኃጣውኢከ ቅድመ ከመ ትጽደቅ - ትከብር ዘንድ አንተ አስቀድመህ ኃጢአትህን ተናገር” ይላል (ኢሳ.43፡26)፡፡ [ስለዚህ] ኃጢአትህን ታስወግዳት ዘንድ ተናዘዛት፡፡

ይህን ለማድረግ ውጣ ውረድ የለውም፤ ዙሪያ ጥምጥም የቃላት ድርደራም አያሻህም፤ ገንዘብ መክፈል አያስፈልግህም፤ ወይም እነዚህን የመሰሉ ሌሎች ነገሮች አያስፈልጉህም፡፡ አንዲት ቃል ተናገር፤ በደልህን በአንቃዕድዎ አስባት፤ “በድያለሁ” ብለህም ተናዘዛት፡፡

(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)

t.me/menfesawigetem
1.4K viewslog out, 10:28
Abrir / Cómo
2023-05-12 09:59:17
"እመብርሃን መመኪያችን " ዘማሪ ቀሲስ ብርሃን እሸቱ

በማርያም ሼር link አድርጉ

t.me/menfesawigetem
1.4K viewsWÊÑDÏ , edited  06:59
Abrir / Cómo
2023-05-12 09:59:09 NEW አዲስ ዝማሬ " ፋኑኤል " ዘማሪ ዲያቆን አዳነ ገብረ መስቀል @-mahtot
1.3K viewsWÊÑDÏ , 06:59
Abrir / Cómo
2023-05-12 09:59:09
NEW አዲስ ዝማሬ " ፋኑኤል " ዘማሪ ዲያቆን አዳነ ገብረ መስቀል @-mahtot
1.3K viewsWÊÑDÏ , 06:59
Abrir / Cómo