Get Mystery Box with random crypto!

መንፈሳዊ ኪነ-ጥበብ💒

Logotipo del canal de telegramas menfesawigetem - መንፈሳዊ ኪነ-ጥበብ💒
Logotipo del canal de telegramas menfesawigetem - መንፈሳዊ ኪነ-ጥበብ💒
Dirección del canal: @menfesawigetem
Categorías: Religión
Idioma: Español
Suscriptores: 9.70K
Descripción del canal

በተለያዩ ሰዎች የተፃፋትን መንፈሳዊ ግጥም እና ታሪክ የኪነጥበብ ፅሁፎችን መንፈሳዊ profile Picture አሰተማሪ ታሪኮችን የሚያገኙበት channel ነው👈

በሰነፍ ጆሮ አንዳች አትናገር፣የቃልህን ጥበብ ያፌዝብሀልና። ምሳሌ 23፥9

መንፈሳዊ ግጥም ታሪክ ጭውውት ድራማ ለመላክ
t.me/abrex_1 @yemaryamlj1
ላይ መላክ ይቻላል አሰተያየት እንቀበላለን

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


Los últimos mensajes

2023-05-17 07:36:56 መንፈሳዊ ኪነ-ጥበብ pinned «#ስምና_ትርጉሞቻቸው 1መልከጼዴቅ =#የፅድቅ ንጉስ 2ኑሀሚን =#ደስታ 3ምናሴ =#ማስረሻ 4ዮሴፍ =ይጨመርልኝ ,ይደገመኝ 5ሰሎሞን =#ሰላማዊ 6መክብብ =#ሰባኪ 7ኢሳይያስ =እግዚአብሔር ፈራጅ ነው 8ኤርሚያስ =እግዚአብሔር ከፍ ያደርጋል 9ሕዝቅኤል =ብርታትን ይሰጣል 10ዳንኤል =#ዳኛ ነው 11ሚክያስ =የሚመስለው ማን ነው 12ሶፎንያስ =#ከለላ ነው 13ኢዩኤል =#አምላክ ነው 14ዘካርያስ =(ያስታውሳል…»
04:36
Abrir / Cómo
2023-05-16 21:59:52 ምክንያትህን አሸንፍ !

ቆንጆ እድል ምክንያትን ትጋብዛለች ልክ የሆነ መልካም ነገር ስናገኝ እርሱን እንዳንጠቀምበት ወይም ይበልጥ እንድንበረታ የሚያደርግ ነገር ይፈጠራል እና ግን ከምክንያቱ በላይ ስንሆን ህይወት ከጠበቅነው በላይ ብሩህ ይሆናል !

"አንድ እርምጃ አንድ ለውጥ ነው እና ሁሌም ከለውጡ ጋር ተራመድ "

ቆንጆ ምሽት ተመኘን
InspireEthiopia
478 viewssee you, 18:59
Abrir / Cómo
2023-05-16 12:41:53 #ስምና_ትርጉሞቻቸው

1መልከጼዴቅ =#የፅድቅ ንጉስ
2ኑሀሚን =#ደስታ
3ምናሴ =#ማስረሻ
4ዮሴፍ =ይጨመርልኝ ,ይደገመኝ
5ሰሎሞን =#ሰላማዊ
6መክብብ =#ሰባኪ
7ኢሳይያስ =እግዚአብሔር ፈራጅ ነው
8ኤርሚያስ =እግዚአብሔር ከፍ ያደርጋል
9ሕዝቅኤል =ብርታትን ይሰጣል
10ዳንኤል =#ዳኛ ነው
11ሚክያስ =የሚመስለው ማን ነው
12ሶፎንያስ =#ከለላ ነው
13ኢዩኤል =#አምላክ ነው
14ዘካርያስ =(ያስታውሳል
15ሚልክያስ =#መልዕተኛ
16ዮናስ =#ርግብ
17ናሆም =#መፅናናት
18እንባቆም =#ማቀፍ
19ሀጌ =#የኔ ደስታ
20ማቴዎስ =#ስጦታ
21ማርቆስ =ካህን ,ልዑክ
22ሉቃስ =#ብርሀን
23ዮሐንስ =#ፍስሀወሀሴት
24ያሬድ =ርደት, መውረድ
25በርተሎሜዎስ =አትክልተኛ
26ሕርያቆስ =ረቂቅ ብርሀን
27እስጢፋኖስ =#ፋኖስ
28ባስልዮስ =#መዕቶት
29ማትያስ =#ምትክ
30ዳዊት =#ብላቴና
31ጴጥሮስ =#ዐለት
32 ያዕቆብ =ተረከዝ ያዥ
33 ኢያሱ =#መድሀኒት
34ይሁዳ =#ታማኝ
35አርዮስ =#ፀሀይ
36ሙሴ =#የዋህ
37አብርሀም =የብዙዎች አባት
38ሳሙኤል =ፀሎቴን ሰማኝ
39ኢዮብ =#አበባ
40ሲራክ =#ፀሀፊ
41ጳውሎስ =ምርጥ ዕቃ
42ኢየሱስ =(መድሀኒት
43 ክርስቶስ =#ንጉስ
44 ኤልሻዳይ =ሁሉን ቻይ
45. ዮሐንስ = የእግዚአብሔር ፀጋ (ሀሴት፣ ፍስሀ)
45. ዳንኤል = እግዚአብሔር ፈራጅ ነው
46. ኤልሳዕ =እግዚአብሔር ደህንነት
47. አሞን =#የወገኔ ልጅ
48. እስራኤል =የእግዚአብሔር ህዝቦች
49 ማርያም = የእግዚአብሔር ስጦታ
50. ሀና =#ፀጋ
51. ሩሀማ =ምህረት የሚገባት
52. ኢ ያሱ =እግዚአብሔር አዳኝ ነው፣ መድሃኒት
53. ጌርሳም=ከሌላ ምድር ስደተኛ ነኝ
54. እዮሳፍጥ=እግዚአብሔር ፈርዷል
55. እዮአም =#አዳኝ
56. ኢዮሲያስ= ከፍ ከፍ አለ
57. ኤልሳቤጥ= እግዚአብሔር መሀላዬ ነው
58. አብርሃም = የብዙሃን አባት
59. ኢሊዲያ ( ይድድያ ) = በእግዚአብሔር የተወደደ
60. ኤዶንያስ =እግዚአብሔር ጌታዬ ነው
61. ኦዶኒራም= ጌታየ ከፍ ያለ ነው አለ
62. ሆሴዕ= እግዚአብሔር መድኃኒት ነው
62. ሕ ዝቅያዝ = እግዚአብሔር ሀይሌ ነው
63. ጴጥሮስ=# መሰረት
64. ሴት =#ምትክ
65. ሳሙኤል =እግዚአብሔርን ለምኜዋለው
66. አቤል =የህይወት እስትንፋስ
67. ጎዶሊያስ =እግዚአብሔር ታላቅ ነው
68. ስጥና =# ተዘጋ
69. ማቴዎስ =#ሞገስ
70. ፌቨን=# የእግዚአብሔር አገልጋይ
71. ሚኪያስ =እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን አለ
72 ይሁዳ= አማኝ ( የአማኝ ልጅ)
73. ወንጌል = የምስራች
74. ኤርሚያስ=እግዚአብሔር ከፍ ከፍ ያደርጋል
75. ህዝቅኤል = እግዚአብሔር ብርታት ይሰጣል
76. ማራናታ= እግዚአብሔር ቶሎ ና
77.ሆሴዕ =እግዚአብሔር ያድናል
78. አሞፅ =#ሀይል
79. ኤሴቅ =#የተጣላሁብሽ
80. ሚኪያስ =እግዚአብሔር የሚመስል ማን ነው
81. ኢ ዮኤል=እግዚአብሔር አምላክነው
82. አብድዩ=የእግዚአብሔር አገልጋይ
83. ዮናስ =#ርግብ ( የዋህ፣እሩሩህ )
84.እምባቆም = እቅፍ
85. ሶፎኒያስ =እግዚአብሔር ጠብቋል
86.ሀጌ=በሀላዊ ወይም በበዓል የተወለደ
87. ዘካርያስ =እግዚአብሔር ያስታውሳል
88. ሚልክያስ ፡- መልክተኛዬ
89. ናታኔም ፡ - የእግዚአብሔር ጠራጊ
90. አቤኔዘር ፡ - እግዚአብሔር እረድቶኛል

1. ~ሆሴዕ - እግዚአብሔር ያድናል
2. ~ሐና - ጸጋ
3. ~ሔዋን - የሕያዋን ሁሉ እናት
4. ~ሕዝቅኤል- እግዚአብሔር ብርታትን ይሰጣል
5. ~ሕዝቅያስ - እግዚአብሔር ኃይል ነው
6. ~መልከ ጼዴቅ - የጽድቅ ንጉሥ
7. ~ሚልክያስ - መልእክተኛየ
8. ~ሚክያስ - እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው
9. ~ምናሴ - ማስረሻ
10. ~ሣራ - ልዕልት
11. ~ሩሐማ - ምህረት
12. ~ሮቤል - እነሆ ወንድ ልጅ
13. ~ሰሎሞን - ሰላማዊ
14. ~ሳሙኤል - አምላካዊ ስም (የአምላክ ስም)
15. ~ሳኦል - ከእግዚአብሔር የተለመነ
16. ~ሴዴቅያስ - የእግዚአብሔር ጽድቅ
17. ~ሶፎንያስ - እግዚአብሔር ሰውሯል
18. ~ቃዴስ - ቅዱስ
19. ~በርተለሜዎሰ - የተለሜዎስ ልጅ
20. ~በንያስ - እግዚአብሔር አዳነኝ
21. ~ባሮክ - ቡሩክ
22.~ ቤተልሔም - የእንጀራ ቤት
23. ~ቤተል - የእግዚአብሔር ቤት
24. ~ብንያም - የቀኝ እጄ ልጅ (የደቡብ ልጅ)
25. ~ቶማስ - መንታ
26. ~ናሆም - መጽናናት
27. ~ናታን - እግዚአብሔር ሰጥቷል
28. ~ንፍታሌም - የሚታገል
29. ~አልዓዛር - እግዚአብሔር ረድቷል
30. ~አማኑኤል - እግዚአብሔር ከእኛጋር
31. ~አርኤል - የእግዚአብሔር ምድጃ
32. ~አሴር - ደስተኛ
33. ~አስቴር - ኮኮብ
34. ~አብርሃም - ታላቅ አባት (የብዙዎች አባት)
35. አቤሴሎም - አባቴ ሰላም ነው
36. ~አቡ - አባት
37. ~አብዱዩ - የእግዚአብሔር አገልጋይ
38.~ አቢያ - እግዚአብሔር ወንድሜ ነው
39. ~ኢሳይያስ - እግዚአብሔር ደህንነት ነው
40. ~አቤኔዘር— እግዚአብሔር እረድቶኛል
41.~ ኢዩኤል - እግዚአብሔር አምላክ ነው
42. ~ኢያሱ - እግዚአብሔር አዳኝ ነው
43. ~ኢይዝራኤል - እግዚአብሔር ይዘራል
44.~ ኢዩሣፍጥ - እግዚአብሔር ፈርዷል
45. ~ኢዩራም - እግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ
46. ~ኢዩርብአም - ሕዝቡ እየበዛ ሄደ
47. ~ኢዮስያስ - እግዚአብሔር ይደግፋል
48.~ ኢዮአስ - እግዚአብሔር ሰጥቷል
49.~ ኢያቄም - እግዚአብሔር አቆመ
50. ~ኢዮአብ - እግዚአብሔር አባቴ ነው
51.~ ኢዮአታም - እግዚአብሔር ፍጹም ነው
52. ~ኢዮአካዝ - እግዚአብሔር ይዟል
53. ~ኤሊዔዘር - እግዚአብሔር ረዳቴ ነው
54.~ ኤልሳዕ - እግዚአብሔር ደህንነት ነው
55.~ ኤልያቄም - እግዚአብሔር ያስነሳል
56. ~ኤርምያስ - እግዚአብሔር ከፍ ያደርጋል
57. ~እስማኤል - እግዚአብሔር ይሰማል
58. ~ኬልቅያስ - እድል ፈንታየ እግዚአብሔር ነው
59. ~ኤድን - ደስታ
60. ~ኬብሮን - ኅብረት
61.~ ዘካርያስ - እግዚአብሔር ያስታውሳል
62. ~ይሳኮር - ዋጋየ
63. ~ይዲድያ - በእግዚአብሔር የተወደደ
64. ~ዮሐናን - እግዚአብሔር ጸጋ ሰጭ ነው
65. ~ዮናስ - ርግብ (የዋህ)
66. ~ዮናታን - እግዚአብሔር ሰጥቷል
67. ~ዮአኪን - እግዚአብሔር ያቆማል
68.~ የካብድ - እግዚአብሔር ክብር ነው
69. ~ዮዳሄ - እግዚአብሔር ያውቃል
70. ~ዮፍታሔ - እግዚአብሔር ይከፍታል
71. ~ጋድ - መልካም ዕድል
72.~ ጎዶልያስ - እግዚአብሔር ታላቅ ነው

pls share link

@menfesawigetem
1.8K viewssee you, edited  09:41
Abrir / Cómo
2023-05-15 16:24:43 ስለ እውነት የሚማሩበት ታሪክ


አንድ አባት ለልጁ የሚጣፍጥ ምግብ አዘጋጀለትና በመሶብ አድርጎ አቀረበለት፤ ልጁም እንጀራውን እስኪጠግብ በልቶት መሶቧን ወረወራት። አባቱ "ልጄ ለምን ወረወርካት " ብሎ ጠየቀው። ልጁም "ምን ታረግልኛለች
እንጀራውንስ በላው" አለ። አባቱም "ልጄ ነገ ምናልባት እንጀራ ባይርብህም ግን ችግር ሊደርስብህ ይችላል በዛን ጊዜ ይህችን መሶብ ይዘህ ለምስክርነት ከዝህች መሶብ የበላው ሰው ነበርኩ ዛሬ ግን ቸግሮኝ ለልመና ወጣው ትላለህ መሶቧን ሳትይዝ ብትወጣ ግን ማጅራት መቺ ዱርዬ ነህ ብለው ይደበድቡሃል ልጄ ስለዚህም መሶቧ ታስፈልግሃለች" አለው። ልጁም "አይ አባቴ አታስፈልገኝም" ብሎ መለሰለት። ያን ጊዜ አባቱም "ልጄ በስሜ ትጠራ ይሆናል ነገር ግን የኔ ልጅ አይደለህም ያበላችህን ቀኜን ክደሃታልና እኔ በዝህች መሶብ
ከብሬ አንተ ግን እሷን ካድካት" አለው።
   
አባት የተባለው አብ ነው ፤ እንጀራ የተባለው ወልድ ነው፤ መሶብ የተባለችው ድንግል ማርያም ናት። 'አብ አንድ ልጁን አሳልፎ እስኪሰጥ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና' ተብሎ እንደተፃፈ! ወልድም 'የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ'
እንዳለ ስለድንግል ማርያም 'ሰው ሁሉ እናታችን ጽዮን ይላታል በውስጧ ሰው ተወልዷልና' እንደተባለ። አንተም አብ በልጁ እንድትድንበት ብሰጥህ ዳንኩኝ በቃ ብለህ ለመዳንህ ምክንያት የሆነችውን ድንግልን ካድካት። ርሃብ ባያጋጥምህ እንኳን ለሌላ ችግር ትጠቅምሃለች የተባለው አንተ ሰው ነህ በምትሰራው ኃጢአት ሁሉ ስለእናትህ ብለህ ማረኝ ብትለው ጌታ ይምርሃል እናቱንም አንቺ ታስፈልግኛለሽ አማላጄ ብትላት ሁሉ ሙሉ ይሆንልሃል።
@eotcy
አንተ ግን ይህን ሁሉ አልቀበል አልክ። አባት ልጁን በስሜ ትጠራለህ ግን ልጄ አይደለህም እንዳለ አንተም ዛሬ በኢየሱስ ስም ትጠራለህ ነገር ግን የእርሱ ልጅ አይደለህም አባትህን አንተም ታውቀዋለህ ማን እንደሆነ! ያለ መሶብ እንጀራ እንዳሌለ ሁሉ ያለ ድንግል ማርያምም ክርስቶስ የለም።

በማርያም ሼር link አድርጉ

join

@menfesawigetem
1.4K viewssee you, edited  13:24
Abrir / Cómo
2023-05-14 19:37:57 አንድ ሰው መጥቶ እናንተ የምትለብሱትን አንዲት ቁራጭ ልብስ እንኳ ሳይሰጣችሁና ሰውነታችሁ በብርድና በዋዕየ ፀሐይ እየተቆራመደ ሳለ ቤታችሁን በወርቅና በተንቆጠቆጠ የመጋረጃ ዓይነት ቢያስጌጥላችሁ ምን ጥቅም አለው? እኛስ ነፍሳችን ዕራቁቷን ሳለች ሥጋችንን ወርቅ ብናለብሰው በወርቅ ብናስተኛው ምን ትርጉም አለው? ነፍሳችን በመሬት ላይ እየተንፏቀቀች ሳለ ሥጋችን በከበሩ ሠረገላዎችና የተለያዩ ማጓጓዣዎች ብትንፈላሰስ ምን ጥቅም አለው?

ልጆቼ ! እውነተኛውን ልብስ ልበሱ ብዬ እመክራችኋለሁ። እዚህ የሚቀረውን ሳይኾን ዘለዓማዊውን ልብስ ልበሱ። የሰርጉን ልብስ ልበሱ።

እስኪ በየገዳማቱ ሒዱና ይህን ከቅዱሳን አበው ወእማት ተማሩ። እነዚህ ቅዱሳን በእልፍ ወትእልፊት ዕንቁ የተሽቆጠቆጠ ልብስ ብትሰጥዋቸው አይቀበሏችሁም። ለምን? እነርሱ ጋር ያለው ልብስ እናንተ ይዛችሁት ከሔዳችሁት ይልቅ በእጅጉ እንደሚበልጥ ስለሚያውቁ! ይኸውም የነፍሳቸው ልብስ ማለቴ ነው።

ለእነርሱ ይዛችሁት የሔዳችሁት ልብስ ለአንድ ምድራዊ ንጉሥ ብትሰጡት እጅግ ያመሰግናችኋል። እነርሱ ግን ከዚህ ንጉሥ በላይ በከበረ ልብሱ ያጌጡ ናቸውና አይቀበሏችሁም። ወርቃቸውን ወደሚያስቀምጡበት መዝገብ (ልቡናቸው) ገብታችሁ ስታዩ'ማ ራሳችሁን ስታችሁ ትወድቃላችሁ ። የሀብታቸውን (ምግባር ትሩፋታቸውን) ብዛት የወርቃቸውን ንጻት እንዲህ ነው ተብሎ የሚነገር አይደለም ። እናንተም ከእነርሱ ተማሩና እውነተኛውን ልብስ ለመልበስ ተሽቀዳደሙ ።

#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
ሰማዕትነት አያምልጣችሁ መጽሐፍ
1.5K viewsBirta, 16:37
Abrir / Cómo
2023-05-14 14:07:10 *የሰንበትን ቀን ትቀድሳት ዘንድ አስብ*

*ይህች ታላቅ ትዕዛዝ ከ፲ቱ ትዕዛዝ አንዷ ናት። አትስረቅ፣ አትግደል፣ አታመንዝር ከሚሉት ሕግጋት እኩል ናት። እናስተውል።*

*መድኃኒታችን ሰው የሆነባት ሰንበተ ክርስቲያን: ዕለተ እሁድ ብርሃን ናት:: ይህች ሰንበት ጌታችን ከሙታን ተለይቶ ተነሳባት:: መንፈስ ቅዱስም በጽርሐ ጽዮን ወረደባት፣ በህያዋን እና በሙታን ለመፍረድም አምላካችን ዳግም የሚመጣባት ታላቅ ዕለት ናት እናም እባክህን አክብራት: ዛሬ በሰንበት የት ነህ? ዛሬ በሰንበት የት ነሽ? የት ነን?*

*ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት በሦስት ቀን አነሳዋለሁ እንዳለ ቅድስት ቤተክርስቲያን የታነጸችበት ዕለተ እሁድ ብርሃን ናት::*

*ድርሳነ መድኃኔዓለም*

*ከቀናት ሁሉ ክርስቶስ መርጦ የተወለደባት፣ የተጠመቀባት፣ ለሰው ልጅ ድህነትን፣ የሰጠባት ትንሣኤውንም የገለጠባት ይህቺ እሁድ ሰንበተ ክርስቲያን ናት::*

*ሰባተኛው ቀን ግን ለእግዚአብሔር ለአምላክህ ሰንበት ነው፤ አንተ፥ ወንድ ልጅህም፥ ሴት ልጅህም፥ ሎሌህም፥ ገረድህም፥ ከብትህም፥ በደጆችህም ውስጥ ያለ እንግዳ በእርሱ ምንም ሥራ አትሥሩ፤*

*እግዚአብሔር በስድስት ቀን ሰማይንና ምድርን፥ ባሕርንም፥ ያለባቸውንም ሁሉ ፈጥሮ በሰባተኛው ቀን ዐርፎአልና፤ ስለዚህ እግዚአብሔር የሰንበትን ቀን ባርኮታል ቀድሶታልም* ። ዘጸአት 20:10

*እግዚአብሔር ሰንበቴን ስለሚጠብቁ ደስ የሚያሰኘኝንም ነገር ስለሚመርጡ ቃል ኪዳኔንም ስለሚይዙ ጃንደረቦች እንዲህ ይላልና። በቤቴና በቅጥሬ ውስጥ ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች ይልቅ የሚበልጥ መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋለሁ፤ የማይጠፋም የዘላለም ስም እሰጣቸዋለሁ። ያገለግሉት ዘንድ የእግዚአብሔርንም ስም ይወድዱ ዘንድ ባሪያዎቹም ይሆኑ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር የሚጠጉትንም መጻተኞች፥ እንዳያረክሱት ሰንበትን የሚጠብቁትን ቃል ኪዳኔንም የሚይዙትን ሁሉ፥ ወደ ተቀደሰ ተራራዬ አመጣቸዋለሁ፥ በጸሎቴም ቤት ደስ አሰኛቸዋለሁ፤*
ትንቢተ ኢሳ 56:4-7

*ወንድሞቼና እህቶቼ ስለዚህም በፍጹም ሰንበትን ተኝታችሁ አታሳልፉ:: ተነሱ፣ ወደ ደጀሰላሙ ድረሱ፣ ጸልዩ፣ አስቀድሱ:: ጸበሉን ጠጡ፣ ጸበል ጸዲቁን ቅመሱ፣ የታመመ የታሰረ የተቸገረ ጠይቁ።*

*በታላቂቷ ሰንበት በማለዳ ወደ ቤተ ክርስቲያን ገስግሱ፣ መስቀሉን ተሳለሙ:: ግድግዳውን መሬቱን ሁሉን ደባብሱ:: ከክርስቲያን ወንድም እህቶቻችሁ ጋር  በመንፈሳዊ ፍቅር ትከሻ ለትከሻ ተሳሳሙ:: ደጉ እግዚአብሔር አባታችሁ ይጠብቃችኋል:: ያድናችኋል:: ሰላሙን ይሰጣችኋል::በዚህች የከበረች ሰንበት ማለዳ የት ነበርን?????????*

*የሰማዕቷ ድስት አርሴማ አማላጅነት የሰንበት ጸጋ እና ረድኤት በያለንበት ይድረስልን።*

ብሩህ  ሰንበት


@menfesawigetem
1.4K viewsWÊÑDÏ , edited  11:07
Abrir / Cómo
2023-05-14 13:15:50 ተሰበበረ ሰንሰለቱ

ተሰባበረ ሰንሰለቱ
መናወጥ ሆነ ወይን ቤቱ
የጌታ ማዳን ተገለጠ
እስረኛው ጴጥሮስ አመለጠ

አዝ......

ደስ ይበላችሁ እናንተ ሐዋርያት
ወንድማችሁ ጴጥሮስ ተፈታ ከእስር ቤት
የምስራች ወንጌል ስበኩ ተግታቹ
ሞትን አሸናፊ አለ ከጎናችሁ

አዝ....

ሁሩ ወመሀሩ ተብላቹሃልና
እንዳትዘናጉ በአለም ፈተና
የመከራ ማህበል ወጀቡን ስታዮ
ትግስቱን ይስጣችሁ ለበጎነው በሉ

ሁሉም ነገር ለበጎ ነው
መከራም ቢሆን ለበጎ ነው

አዝ.....

ከኛ ጋር ያለው ከእነርሱ ይበልጣል
እስር ቤት ተጥለን መቶ አፀናንቶናል
በብርሃን መስቀሉ ጎኔን ጎሽሞኝ
ወደ ፊት ሂድ አለኝ ከእንቅልፌ ቀስቅሶኝ

አዝ.....

ለሰው ከመታዘዝ ለእግዚያብሔር ይሻላል
ለህሊና መኖር ከሁሉም ይበልጣል
እስር ሰንሰለቱን ዱላውን ሳንፈራ
እንመሰክራለን የእውነቱን ስራ

አዝ....

አፅራረ ክርስቶስ እጁን ቢጭንብኝ
ወደ ሃላ አንሄድም መስቀሉን ጨብጠን
ከሞት ቦሃላ ህይወት እንዳለ እናውቃለን
እውነት ለመመስከር እንፈጥናለን

አዝ....

ሁሉም የእርሱ እንደሆነ እኛም የእርሱ ነን
ምስጋናን ለማቅረብ እንተጋለን
ምድር ተናወጠች በዝማሬ ዜማ
ሰንሰለቱ ወደቀ መዝሙሩ ሲሰማ

አዝ....

አትደንግጪ ያንኳካው ጴጥሮስ ነው
ሚካኤል ልኮት ጌታ ነው የፈታው
መዝጊያውን ክፈቺ ወዴት ትሄጃለሽ
ደስታችን ለመግለጥ ዝም በይ ትደርሻለሽ

አዝ....

የሐዋርያት ፀሎት እጅጉን ይጠቅማል
ከእስር ከሰንሰለት በእውነት ይታደጋል
በምልጃው በፀሎት ደግሞም በምስጋና
እስከ መጨረሻው እንፀናለን ገና

ተሰባበረ ሰንሰለቱ
ዘማሪት አዜብ ከበደ
ዘማሪ ቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ


pls share link

@menfesawigetem
1.2K viewsWÊÑDÏ , edited  10:15
Abrir / Cómo
2023-05-14 13:15:49
ተሰባበረ ሰንሰለቱ ዘማሪት አዜብ ከበደ እና ዘማሪ ቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ
932 viewsWÊÑDÏ , 10:15
Abrir / Cómo
2023-05-14 13:14:24 #ሰንበተ_ክርስትያን

በኩር ናት የበዓላት
ኑ ከፍ ከፍ እናድርጋት
በእሷ ደስ ይበለን
በሰንበተ ክርስቲያን

በዝማሬ እንበርታ በገናውን እንያዝና
መልካም ስራ የሚሰራባት
ሰንበት ቅድስት ናት እና
ከጨለማ ብርሀን ከመገዛት ነፃነት
እግዚአብሔር ይህን ሰጠን
ደስ ይበለን በሰንበት
#አዝ
ለአብርሃም ተገልጣለች
ለሙሴም በደብረ ሲና
በነቢያት የታወቀች
ሰንበት ዳራዊት ናት እና
በሳምንቱ ሰለጠነች
ተሰበከች በሐዋርያት
ሃሌ ሉያ ዕለተ ሰንበት
ተሰጠችን ልናርፍባት
#አዝ
በእልልታ እንሞላ እንደ ነቢዩ አሳፍር
በከበረች የሰንበት ቀን ኑ ለቅኔ እንሰለፍ
በመቅደሱ ናቸው እና ቅዱስነትና ግርማ
ውዳሴያችን ይሰማልን
ከምድር እስከ እዮር እራማ
#አዝ
እግዚአብሔር አብ የባረካት
እግዚአብሔር ወልድ የቀደሳት
ከእለታት ሁሉ መርጦ
መንፈስ ቅዱስ ከፍ ያደረጋት
በእርሷ ሀሴት እናድርግ
እናክብራት እንድንከብር
የደጀሰላሙ ታዛ በመቅደሱ እንሰብሰብ

@menfesawigetem
881 viewssee you, edited  10:14
Abrir / Cómo
2023-05-14 12:59:10 ​​✟✞✟አላፍርም እኔ በማርያም✟✞✟

አላፍርም እኔ በማርያም
አላፍርም እኔ በማርያም
ሥሟን ሥጠራት እጽናናለሁ
የሐዘኔ መርሻ ብያታለሁ/፪/

/አዝማች/

ሥሟን ስጠራት በሐዘኔ ጊዜ
አጽናንታኛለች ይዞኝ ትካዜ
የመከራ ቀን የጭንቀት ደራሽ
እንደ አንቺ የለም እመቤቴ ነሽ
ማርያም ማርያም በሉ ምዕመናን ሁሉ
ማርያ ማርያምብለን እንድናለን

/አዝማች/

አደጋ ጣዮች ደርሰው ድንገት
ሥም አጠራሬን ሁሉም ጠልተውት
መታወቂያዬ አንቺ ነሽና
ሥዕልሽን ሲያዩ ጠፉ እንደ ገና
ማርያም ማርያም በሉ ምዕመናን ሁሉ
ማርያ ማርያም ብለን እንድናለን

/አዝማች/

የአሰብሁት ሁሉ በጅምር ቀርቶ
አንጋጥጣለሁ ዘመኑ በዝቶ
ፍጻሜን እንዳይ ድንግል እርጅኝ
ደጅሽ ወድቄ ተማጸንሁኝ
ማርያም ማርያም በሉ ምዕመናን ሁሉ
ማርያም ማርያም ብለን እንድናለን

/አዝማች/

አደጋ ጣዮች ደርሰው ድንገት
ሥም አጠራሬን ሁሉም ጠልተውት
መታወቂያዬ አንቺ ነሽና
ሥዕልሽን ሲያዩ ጠፉ እንደ ገና
ማርያም ማርያም በሉ ምዕመናን ሁሉ
ማርያም ማርያም ብለን እንድናለን።


በማርያም ሼር ሊንክ አድርጉ

t.me/menfesawigetem
943 viewsWÊÑDÏ , edited  09:59
Abrir / Cómo